Established

1327 E.C.

Location

11°51′N 38°1′E

Population

180,000

Elevation

2,706 mt.
(8,878 ft.)

Debre Tabor (Amharicደብረ ታቦርlit. “Mount Tabor”) is a town and woreda in north-central Ethiopia. Located in the Debub Gondar Zone of the Amhara Region, about 100 kilometers southeast of Gondar and 50 kilometers east of Lake Tana, this historic town has a latitude and longitude of 11°51′N 38°1′E with an elevation of 2,706 metres (8,878 ft) above sea level. The presence of at least 48 springs in the area contributed to the development of Debre Tabor.

 

የታቦር ተራራን መነሻ በማድረግ ስያሜዋን ያገኘችው ደብረታቦር በኢትዮጵያ ጥንታዊና ታሪካዊ ከሚባሉ ከተሞች መካከል አንዷ ናት።

ደብረታቦር የጥንት የበጌምድር መናገሻ ከተማ የነበረች በኋላም በዘመነ መሳፍንትና ከዘመነ መሳፍንት በኋላ በነገሱት የአጼ ቴዎድሮስ እና አጼ ዮሀንስ ዘመነ መንግስት ወቅት የኢትዮጵያ ዋና ከተማ በመሆን ያገለገለች ጥንታዊና ታሪካዊ ከተማ ናት።

ከተማዋ በ1327 ዓ/ም በአጼ ሰይፈ አርዕድ አማካኝነት እንደተቆረቆረች ይነገርላታል። ከዚህ ዘመን በኋላ ከተማዋ በርካታ ሂደቶችን አልፋለች። በቀደመ ስሟ ጁራ/ሰማራ እየተባለች ትጠራ እንደነበርና ነዋሪዎችም እጅግ ታታሪ ሰራተኞችና ጥበበኞች እንደሆኑ ይነገርላቸዋል።

ደብረታቦር የበጌምድር ጠቅላይ ግዛት ገዥ በነበሩት በራስ ጉግሣ ወሌ ዘመን የከተሜነት ቅርጿ የዘመነና ኢትዮጵያ ውስጥ ሞቅ ያለ የገቢያ ስርአትና የህዝብ እንቅስቃሴ ከሚታይባቸው ከተሞች መካከል አንዷ እንደሆነች የታሪክ ድርሳናት ያሳያሉ።

ደብረታቦር የመጀመሪያው የኢትዮጵያ የቴክኖሎጂ ጥማት ማስታገሻ፣ የአጼ ቴዎድሮስ የህልም መወጠኛ የመጀመሪያው የጋፋት የኢንዱስትሪ መንደር መገኛ ከተማ ናት። ደብረታቦር በርካታ ምንጮች ይገኙ እንደነበርና በተለይም ከ1890ዎቹ ጀምሮ የባህርዛፍ ተክል ወደ ኢትዮጵያ መግባቱን ተከትሎ ብዙዎቹ ምንጮች እንደተዳከሙ ይታወቃል። ከደብረታቦር በቅርብ እርቀት የአፍሪካ የውሃ ማማ የሆነው የጉና ተራራ ይገኝበታል። የጉና ተራራ ከአራት መቶ በላይ ምንጮችና ከ40 በላይ ወንዞችን ይወጡበታል። ከጉና ወጥተው ለአባይ የውሃ መሰረት የሆኑት የጣና ገባር ወንዞች ከሆኑት ርብና ጉማራ መካከል ይጠቀሳሉ።

ደብረታቦር የአጼ ዮሀንስ 4ኛ ቤተመንግሥት ሰመርንሃም ይገኝባታል። አጼ ዮሀንስ 4ኛ በነገሱበት ወቅት በክረምት ወቅት ቤተመንግስታቸውን ደብረታቦር ሰመርንሀ በማድረግ ያሳልፉ እንደነበር የታሪክ ድርሳናት ይገልጻሉ።